በኮንሶ ዞን ለተከታታይ አራት የመኸር ዘመን ተቋርጦ የነበረው ዝናብ ባስከተለው ሰብአዊ ቀውስ ምክንያት ቢያንስ 190 ሺሕ ሰዎች አስቸኳይ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን ሁኔታ አስመልክቶ ትናንት ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት አስታውቋል
ኮሚሽኑ ክትትል ባደረገባቸው ቦታዎች ከታዩ መለስተኛ የምርጫ አስተዳደር ግድፈቶች ውጭ አጠቃላይ ሕዝበ ውሳኔው ሰላማዊ፣ ሥርዓታዊ እና ከጎላ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ነጻ የነበረ ነው
ከሰብአዊ መብቶች አኳያ ሊቀጥሉ እና ሊበረታቱ የሚገባቸው መልካም አሠራሮች ቢኖሩም የአረጋውያን መንከባከቢያ ማእከላቱ በአብዛኛው ቋሚ የገቢ ምንጭ የሌላቸው እና በገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ያላቸው ተሳትፎም ውስን መሆኑ አገልግሎታቸውን ለማስቀጠልና ዘላቂነቱን (sustainability) ለማረጋገጥ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል
በወልቂጤ ከተማ ለውሃ አቅርቦት ጥያቄ አደባባይ በወጡ ነዋሪዎች ላይ ያልተመጣጠነ፤ ኃይል ተጠቅሞ ጥቃት በማድረስ ሕይወት እንዲጠፋና የአካል ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተጠያቂ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ
ተመሳሳይ ዓይነት የመብት ጥሰቶች እንዳይፈጸሙ ለጸጥታ ኃይሎች ግልጽ አመራር ማስተላለፍ ያስፈልጋል
በጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የተካሄደው ይህ ሕዝበ ውሳኔ ኮሚሽኑ ክትትል ባደረገባቸው 186 ጣቢያዎች ከታዩ መለስተኛ የምርጫ አስተዳደር ግድፈቶች (minor electoral irregularities) ውጪ፤ አጠቃላይ ምርጫው ሰላማዊ፣ ሥርዓታዊ እና ከጎሉ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ነጻ የነበረ ነው
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ እንዳሉት፣ ሕዝበ ውሳኔ የተለያዩ የፖለቲካ አመለካከቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚስተናገዱበት እና ዜጎች በሕዝባዊ ጉዳዮች የመሳተፍ መብታቸውን የሚተገብሩበት አንደኛው ሂደት መሆኑን ገልፀዋል
ምርጫ ጣቢያ ላይ የተፈፀመው የሕግ ጥሰት እስኪጣራ ድረስ ድምጽ የመስጠት ሂደቱ እንዲቋረጥ ተወስኗል
ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች የተስተዋሉ በጎ ጅማሮች እንዲቀጥሉና ኮሚሽኑ ለእርምት እና ለማስተካከያ ያቀራባቸው ምክረ ሃሳቦች እንዲተገበሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል
ኢሰመኮ በሕዝበ ውሳኔው ወቅት የሰብአዊ መብቶች አጠባበቅን የሚከታተል የባለሙያዎች ቡድን ወደ ቦታው አሰማርቷል