Skip to content
Facebook Twitter YouTube Linkedin Flicker
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Human Rights Monitoring and Investigation
        • Women’s and Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

ኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች፡ በተከሰተው ድርቅ በኢሰመኮ የክትትል ሪፖርት የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች ተጠናክረው ሊተገበሩ ይገባል

May 26, 2023August 28, 2023 Press Release, Report

የአተገባበር ክትትል በተሠራበት በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እና በሶማሌ ክልል የተለዩ ቦታዎች ዝናብ መዝነቡ የድርቁ አደጋ ማብቂያ ተደርጎ መወሰድ የለበትም

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች የተከሰተውን የድርቅ አደጋ ተከትሎ ከየካቲት 14 እስከ 29 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ በድርቁ ጉዳት ደርሶባቸው እና ለናሙና የተመረጡ አካባቢዎችን በመዘዋወር የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል በማድረግ ያዘጋጀውንና በዓይነቱ የመጀመሪያው የሆነውን ሪፖርት ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓ.ም. ይፋ ማውጣቱ ይታወሳል። በሪፖርቱ ላይ ከፌዴራል፣ ከኦሮሚያ እና ከሶማሌ ክልሎች ከተውጣጡ የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች እንዲሁም ከተለያዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከተውጣጡ ተሳታፊዎች ጋር ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ከተማ እንዲሁም መስከረም 26 ቀን 2015 ዓ.ም. በጅግጅጋ ከተማ የምክክር መድረኮች ተካሂደዋል፡፡ በተደረገው ምክክር በኢሰመኮ የተሰጡ የሪፖርቱ ምክረ ሐሳቦች አተገባበር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት መሆኑ አጽንዖት ተሰጥቷል፡፡ በመሆኑም ኢሰመኮ በክትትል ሪፖርቱ የተሰጡትን ምክረ ሐሳቦች አተገባበር ለመከታተል ከየካቲት 22 እስከ መጋቢት 2 ቀን 2015 ዓ.ም. መረጃዎችን በመሰብሰብ እና ከመስክ ሥራ በኋላም መረጃዎችን በርቀት በመከታተል የአተገባበር ክትትል ሪፖርት አዘጋጅቷል፡፡

በዚህ የአተገባበር ክትትል በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን 40 ቁልፍ መረጃ ሰጭ ግለሰቦች ጋር ቃለመጠይቆችን እና 9 የቡድን ውይይቶችን፣ እንዲሁም በሶማሌ ክልል 38 ቁልፍ መረጃ ሰጭ ግለሰቦች ጋር ቃለ መጠይቆችን እና 6 የቡድን ውይይቶችን፣ በአጠቃላይ 78 ቃለመጠይቆችን እና 15 የቡድን ውይይቶችን በማድረግ መረጃዎች እና ማስረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ በተሰበሰቡ መረጃዎች የምክረ ሐሳቦችን አተገባበር በመዋቅር፣ በሂደት እና በውጤት አመልካቾች ተተንትነዋል፡፡ 

በዚህም መሠረት የአተገባበር ክትትል የተደረገባቸው ቦታዎች በተደጋጋሚ ጊዜያት በድርቅ የሚጠቁ አካባቢዎች ሲሆኑ፣ የድርቁ አደጋ በተለየ መልኩ በመራዘሙ ማለትም ከ3 እስከ 5 የዝናብ ወቅቶች ያልዘነበበት እንዲሁም ሰፊ ቦታዎችን ያካለለ እንደሆነ የክትትሉ ግኝት ያሳያል፡፡ በመሆኑም በማኅበረሰቡ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ላይ የደረሰው ተጽዕኖ ከበፊቱ ጨምሮ ይገኛል፡፡ በሁለቱም ክልሎች በምግብ እጥረት የሚገለጽ በአረጋውያን፣ በነፍሰ ጡር  እና በሚያጠቡ እናቶች እና ሕፃናት ላይ የሚታይ ጉዳት ጨምሯል፡፡ ይህም በአፋጣኝ እንዲተገበሩ ተብለው ከተሰጡት ምክረ ሐሳቦች መካከል የምላሹ በቂነት ከተደራሽነት፣ ከተስማሚነት እና ከተመጣጣኝነት አንጻር ሲገመገም ዝቅተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡

በሂደት እንዲተገበሩ ተብለው ከተሰጡት ምክረ ሐሳቦች መካከል የዘላቂ መፍትሔ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም በተለይ በቦረና ዞን ያለው የፊና ውሃ ልማት ፕሮጀክት አተገባበር የተሻለና የሚበረታታ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

በሁለቱም ክልሎች በአሁኑ ወቅት ዝናብ መገኘቱ በሂደት እንዲተገበሩ በማለት የተሰጡትን የተወሰኑ ምክረ ሐሳቦችን ለመተግበር፣ በተለይም የሕብረተሰቡን መተዳደሪያ ማስፋት እና የዘላቂ መፍትሔ ፕሮጀክቶች ላይ በትኩረት እንዲሠራ የተሻለ ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡ ይህንኑ አስመልክተው የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “በመንግሥት እና መንግሥታዊ ባልሆኑ አካላት እየተተገበሩ ያሉ ምክረ ሐሳቦችና የተወሰዱ እርምጃዎች አበረታች ቢሆኑም፤ አተገባበሩ በተደራሽነቱ፣ በተስማሚነቱ እና በተዛማጅነቱ እየጨመረ ማኅበረሰቡ መልሶ እስከሚቋቋም ድረስ ሊቀጥል ይገባል፤ በአሁኑ ወቅት ዝናብ መገኘቱም የድርቁ አደጋ ማብቂያ ተደርጎ መወሰድ የለበትም” በማለት ጥሪ አቅርበዋል።

ሙሉ ሪፖርቱ እዚህ ተያይዟል
Location Oromia

Related posts

July 26, 2022October 11, 2022 Press Release
ኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች፡ ዘንድሮ በተከሰተው ድርቅ ለተጎዱ ሰዎች እና አካባቢዎች የሚሰጠው ትኩረት እና ምላሽ አሁንም ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባ ነው
February 15, 2022August 28, 2023 EHRC Quote
ኢሰመኮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ የተወካዮች ም/ቤት ማፅደቁን ተከትሎ በእስር ላይ ያሉ ሰዎች እንዲለቀቁ ጠየቀ
May 19, 2023August 28, 2023 Event Update
ኢሰመኮ የግል የጤና ተቋማት የፋይናንስ ተደራሽነት እና የጤና መብት አተገባበር ሁኔታን በተመለከተ ባከናወነው ክትትል ሪፖርት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ
June 6, 2023August 28, 2023 Press Release
የአካል ጉዳተኞችን ትምህርት የማግኘት መብት ለማረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለአካል ጉዳተኞች ተደራሽ እና አካታች ሊሆኑ ይገባል

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on TwitterYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on Linkedin

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Women’s & Children’s Rights
    • HR Monitoring & Investigation
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter YouTube Linkedin Flicker
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.