Skip to content
Facebook Twitter YouTube Linkedin Flicker
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Human Rights Monitoring and Investigation
        • Women’s and Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

ኢሰመኮ በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት በአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ላይ የደረሰውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በተመለከተ በአማራ ክልልና በአፋር ክልል የተለያዩ ከተሞች ባደረገው ክትትል የተገኙ ግኝቶች እና ምክረ ሃሳቦች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄዱ የምክክር መድረኮች

July 22, 2022October 6, 2022 Event Update

አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች በግጭቱ የደረሰባቸውን ከፍተኛ የመብቶች ጥሰት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሰሜን ኢትዮጵያ ከተካሄደው ጦርነት ጋር ተያይዞ በአካል ጉዳተኞች እና በአረጋውያን ላይ የደረሱትን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ለመለየት በአማራ ክልል (ባሕር ዳር፣ ደቡብ ጎንደር ደብረታቦር፣ ሰሜን ወሎ ጋሸና እና ወልድያ) እና በአፋር ክልል (ሰመራ፣ ሎጊያ፣ ዱብቲ እና ጉያህ ቀበሌ) ያከናወነውን የሰብአዊ መብቶች ክትትል ግኝቶች እና ምክረ ሃሳቦች ለማጋራት እና ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኙ ውትወታ ለማድረግ ያለሙ የተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ አካላት የተገኙባቸው ሦስት የምክክር መድረኮችን ሰኔ 23 ቀን 2014 ዓ.ም. በባሕር ዳር፣ በኮምቦልቻ እና በሰመራ ከተሞች አካሂዷል።

በዝግጅቱ ላይ የክትትሉ ግኝቶች እና ምክረ ሃሳቦች ለባለድርሻ አካላት ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ የምክክር መድረኮቹ ተሳታፊዎችም በክትትል ሂደቱ ላይ የተመለከቷቸውን ውስንነቶች፣ ከክትትሉ በኋላ የተከናወኑ እርምጃዎች፣ መካተት አለባቸው ያሏቸውን ምክረ ሃሳቦች እና በግኝቶቹ መሰረት የተሰጡ ምክረ ሃሳቦችን የአፈጻጸም ሂደት በተመለከተ አስተያየቶችና ጥያቄዎች አቅርበዋል።

ተሳታፊዎቹ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ከጦርነቱ በፊት የነበሩበት የከፋ ሁኔታ በጦርነቱ ተባብሶ ለከፋ የሰብአዊ መብት ጥሰት እና ጉዳት መጋለጣቸውን፤ ጦርነቱ በአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ላይ ካስከተለው የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በተጨማሪ የሰብአዊ ድጋፎች አቅርቦትና ፍላጎት አለመመጣጠንን ጨምሮ ለአካል ጉዳተኞች እና ለአረጋውያን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለመሆን፤  በመንግሥት የሚወሰዱ የመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ውስን መሆናቸውን እና የመልሶ ማቋቋም እና የፈጣን ምላሽ አሰጣጥ ሥራዎችን በተመለከተ መንግሥት፣ ኮሚሽኑ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

እንዲሁም ጦርነቱን ተከትሎ ትምህርታቸውን ያቋረጡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች አሁንም ድረስ በቤት   እና በመጠለያ ውስጥ እንደሚገኙ በመግለጽ ይህን ጉዳይ ኮሚሽኑ ሊመለከተውና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የውትወታ ሥራ እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም የምክረ ሃሳቦችን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ኮሚሽኑ ውሳኔ ሰጪ የመንግሥት አካላትን በተመሳሳይ መድረክ በውይይት ማሳተፍ እንዳለበት እና መንግሥታዊም ሆነ መንግሥታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ አካላት እያንዳንዳችው ምክረ ሃሳቦቹን ለማስፈጸም የሚያስችሉ ሥራዎችን በቅርበት እና በጋራ መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ኮሚሽኑ በየዘርፉ በሚያከናውናቸው የሰብአዊ መብቶች ሥራዎች የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን በተመለከተ በመንግሥት ጠንካራ የተጠያቂነት ሥርዓት አለመኖሩን እንደስጋት በማንሳት፤ ተሳታፊዎች በአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ላይ የሚሠሩ የመንግሥት አካላት በጉዳዩ ላይ ከመቼውም ግዜ በላይ ልዩ ትኩረት መስጠት ያለባቸው ወቅት ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል። 

የኢሰመኮ የአካል ጉዳተኞችና የአረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር ርግበ ገብረሐዋርያ አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች በግጭቱ የደረሰባቸውን ከፍተኛ የመብቶች ጥሰት ሁሉም የባለድርሻ አካላት እንዲያጤኑት እና በቀረቡት ምክረ ሃሳቦች መሰረት የመልሶ ማቋቋም ጥረቶች አካል ጉዳተኞችንና አረጋውያንን ያካተቱ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አክለውም ኮሚሽኑ የተሰጡት ምክረ ሃሳቦች ተፈጻሚነት እንዲኖራቸው የበኩሉን እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡

Location Afar

Related posts

September 29, 2022August 28, 2023 Event Update
A team of EHRC visited the South African Human Rights Commission (SAHRC) and other human rights institutions in South Africa
May 22, 2022October 5, 2022 EHRC Quote
በተለያዩ አካባቢዎች በመፈጸም ላይ ያሉ የጋዜጠኞች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎችና የሌሎች ሰዎች እስሮች
February 3, 2022February 6, 2022 Press Release
Stakeholders Consultation to Support the Implementation of the Recommendations of the Joint Investigation Report of EHRC and OHCHR on the Tigray Conflict
May 15, 2022October 5, 2022 Public Statement
Rising tensions and aggravating rhetoric grave risk to human rights situation in Northern Ethiopia

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on TwitterYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on Linkedin

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Women’s & Children’s Rights
    • HR Monitoring & Investigation
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter YouTube Linkedin Flicker
 

Loading Comments...
 

    Search
    Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
    Powered by  GDPR Cookie Compliance
    Privacy Overview

    This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

    Strictly Necessary Cookies

    Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

    If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.