ማንኛውም ሰው መረጃን የመፈለግ፣ የመቀበል እና የማሰራጨት መብት አለው፡፡(ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ፣ አንቀጽ 19)
መረጃ የማግኘት መብት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አካል ነው፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 29
ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሃሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው፡፡
ይህ ነጻነት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ወሰን ሳይደረግበት በቃልም ሆነ በጽሑፍ ወይም በሕትመት፣ በሥነ ጥበብ መልክ ወይም በመረጠው በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ፣ ማንኛውንም አይነት መረጃና ሃሳብ የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት ነጻነቶችን ያካትታል፡፡